ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
BBC News, አማርኛ - ዜና
ዜና
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሳዑዲ አረቢያ በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የበለጠ ተሳትፎ እንዲኖራት ጠየቁ
የኤርትራ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፤ ሳዑዲ አረቢያ እንደ ናይል ተፋሰስ እና ቀይ ባሕር ባሉ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ተሳትፎ እንድታሳድግ እንዲሁም ለቀጣናው ሰላም "ከፍተኛ አስተዋፆ" እንድታደርግ ጠየቁ። ሳዑዲ አረቢያም በእነዚህ "በወሳኝ ቀጣናዊ ጉዳዮች" ላይ ምክክር ለማድረግ ወደ ኤርትራ ልዑክ እንደምትልክ ገልጻለች ተብሏል።
ፕሬዝዳንት ኢሳያስን በሁለት ወራት ወደ ሦስት አገራት የወሰዳቸው ምክንያት ምንድን ነው?
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከጥቅምት 21 አንስቶ አስከ ኅዳር 30 ድረስ ባለው የሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ወደ ሦስት አገራት ተጉዘዋል። ፕሬዝዳንቱ የቀይ ባሕር ዋነኛ ተጎራባች አገራት ወደሆኑት ወደ ግብፅ፣ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያ ተጉዘው ረዘም ላሉ ቀናት እንዲቆዩ ምክንያት የሆናቸው ጉዳይ ምንድ ነው?
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቻናልን ይቀላቀሉ
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቪድዮዎች
ቪዲዮ, "ቢገድሉኝ ይሻል ነበር'፡ የሴቶችን ሕይወት እያበላሸ ያለው የተዘነጋው የአማራ ክልል ጦርነት
ከሁለት ዓመት በላይ የሆነው በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄደው ግጭት ሰላማዊ ሰዎች ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው። ግጭቱ በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እና ሰቆቃ ትኩረትን አላገኘም። ቢቢሲ ለወራት ባካሄደው ክትትል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶች የመደፈር እና የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ መሆናቸውን መረጃ አግኝቷል።
ቪዲዮ, አምስት ዓመት ያስቆጠረው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ዳግም ይቀሰቀስ ይሆን?
በትግራይ የተካሄደው ጦርነት አምስት ዓመት ሆነው። ጦርነቱ ከፍተኛ ውድመት ከማስከተሉም በላይ ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል ውስጥ በርካታ ክስተቶችን ፈጥሯል። ጦርነቱን ያስቆመው የፕሪቶሪያው ግጭት የማቆም ስምምነት ባለፉት ሦስት ዓመታት አንጻራዊ ሰላም አምጥቷል። የሰላም ስምምነቱ ሦስተኛ ዓመት እየተዘከረ ባለበት በዚህ ወቅት የፌደራል መንግሥቱ እና ህወሓት እየተወነጃጀሉ ነው። ይህ መካሰስ ወደ ጦርነት ያመራ ይሆን?
ቪዲዮ, የጋዛ ጦርነት በመካከለኛው ምሥራቅ የፈጠረው የኃይል ሚዛን ለውጥ
ለሁለት ዓመት የተካሄደው የጋዛ ጦርነት 70 ሺህ የሚጠጉ ፍልስጤማውያንን ሕይወት ቀጥፏል። በኢራን እና በእስራኤል መካከል የቀጥታ ጦርነት ምክንያት ሆኗል። ከመካከለኛው ምሥራቅ እየራቀች የነበረችው አሜሪካ በዚሁ ጦርነት ሳቢያ ተጎትታ ወደ ቀጠናው ተመልሳለች። በአንጻሩ ሩሲያ በቀጠናው የነበራትን ይዞታ ለማጣት ተገዳለች። አጋሮቻቸውን የጋዛ ጦርነት ያዳከመባቸው የሶሪያው ባሻር አል አሳድ ከ13 ዓመት የእርስ በርስ ጦርነት በኋላ ከስልጣን ተወግደዋል። ይህ ቪዲዮ የሁለት ዓመቱ የጋዛ ጦርነት ከመካከለኛው ምሥራቅ ባለፈ በመላው ዓለም የፈጠረውን ለውጥ ይዳስሳል።
ቪዲዮ, ኢሉሚናቲዎች መነሻቸው ከየት ነው? እውን ዓለምንስ በምሥጢር 'ይቆጣጠራሉ'?
"ኢሉሚናቲዎች በምሥጢር ዓለምን ተቆጣጥረው አዲስ ሥርዓት ሊዘረጉ ነው" የሚለው መላ ምት ለዓመታት ሲሰማ ቆይቷል። የዚህ ሃሳብ መነሻ በአውሮፓውያኑ 1960ዎቹ የነበረ ልብ ወለዳዊ ክስተት ነው። ባቫሪያን የሚባል ምሥጢራዊ ስብስብ ነበር።ይህም እአአ በ1776 ነበር የተጀመረው። ወግ አጥባቂ እና ክርስቲያን ተቺዎች ግን አልተቀበሏቸውም። ለተወሰነ ጊዜ ጠፍተው በ1960ዎቹ ዳግመኛ አንሰራሩ።
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ስለባሕር በር፣ ስለድርድር እና ስለምርጫ ምን አሉ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለዓመቱ የመጀመሪያውን ከተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። በዚህም በምጣኔ ሀብት፣ በምርጫ፣ በባሕር በር እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ለሰዓታት የዘለቀ ሰፊ ምላሽ ሰጥተዋል። በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኢትዮጵያ መንግሥት ዋነኛ አጀንዳ የሆነው የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ጉዳይን በስፋት አብራርተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የባሕር በር ያጣችበትን ውሳኔ ማን እንዳሳለፈ የሚታወቅ ነገር እንደሌለ እና መንግሥታቸው “የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው” ብሎ እንደሚያምን ተናግረዋል።
አነጋጋሪ ጉዳይ
ኢትዮጵያውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች በአሜሪካ ምን ዓይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው?
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ሥልጣን ከተመለሱ በኋላ በስደተኞች ላይ ያላቸው አቋም መረር ብሏል። በተለይ ሶማሊያውያን ስደተኞችን በተመለከተ ያንጸባረቁት አቋም እና የሰነዘሩት አስተያየት አነጋጋሪ ሆኗል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ንግግር ያሳሰበው ሶማሊያውያንን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያውያንንም ጭምር ነው። በአሜሪካ ጥገኝነት ለማግኘት ጥያቄ አቅርበው በሂደት ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሊያደርጓቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎችን በተመለከተ በአሜሪካ ታዋቂ የሕግ ባለሙያዎች ምክር አላቸው።
ኢትዮጵያ በ2024 የወባ ስርጭት ከተስፋፋባቸው አገራት አንዷ መሆኗን የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ
ኢትዮጵያ በ2024 የወባ ወረርሽኝ በከፍተኛ ሁኔታ ከጨመረባቸው አገራት አንዷ መሆኗን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። ድርጅቱ 47 አገራት ከወባ ነጻ የሚል እውቅና ማግኘታቸውን አስታውሶ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር እና የመን ግን ወረርሽኙ የጨመረባቸው አገራት መሆናቸውን ገልጿል። እንደ አውሮፓውያኑ በ2024 በ80 የወባ ወረርሽኝ በሚከሰትባቸው የዓለም አገራት 282 ሚሊዮን ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን ድርጅቱ ጨምሮ አስታውቋል።
መቀለ ውስጥ ምንድን ነው የተከሰተው? ከበባ፣ ውይይት፣ የድምጺ ወያነ ሥርጭት መቋረጥ፣ ፍንዳታ...
የታጠቁ የትግራይ ኃይል አባላት "ደመወዝ ዘገየብን" በሚል ቅሬታ መቀለ የሚገኘው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሕንጻ ላይ ከበባ መፈጸማቸውን እና ደምጺ ወያነ ቴሌቪዥን ጣቢያን ተቆጣጥረው እንደነበረ ተገለጸ። ታጣቂዎቹ ከክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን አመሻሽ ላይ በከተማዋ ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተሰምቷል።
ግብፅ የሕዳሴ ግድቡን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር "ተጨማሪ ውይይት" እንደማታደርግ አስታወቀች
ታላቁ የሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር "ተጨማሪ ውይይት" እንደማይደረግ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዲላቲ ተናገሩ። ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ ላለፉት 13 ዓመታት የተደረጉ ውይይቶች "አንዳችም መፍትሔ" አላመጡም ብለዋል። ሚኒስትሩ የአገራቸው ጦር በሶማሊያ ስለተሰማራበት ሁኔታም ተጠይቀው ምላሽ ሰጥተዋል።
የኢንተርኔት ዳታን በመቆጠብ የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽን በቀላሉ ማንበብ ይፈልጋሉ?
የቢቢሲ አማርኛን ድረ ገጽ በቀላሉ በመክፈት ዜና እና ታሪኮችን በጽሑፍ ብቻ ያንብቡ!
ከየፈርጁ
ቢቢሲ አማርኛን በዋትስአፕ ላይ ያግኙ
አጃኢብ!
ግመሎችን እና ወርቅ በመሸጥ ሃብት ያካበቱት፣ አሁን ደግሞ ከፊል ሱዳንን የሚቆጣጠሩት ሐምዳን ዳጎሎ
ሞሐመድ ሐምዳን ዳጎሎ ወይም "ሄሜቲ" ከሚመሩት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር በመሆን በአገሪቱ ፖለቲካ ውስጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኑ እና አሁን የአገሪቱን ግማሽ የሚቆጣጠሩ ግለሰብ ናቸው። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ የአገሪቱ ጦር እና አጋሮቹ በምዕራብ ዳርፉር የምትገኘውን የጦሩ መቀመጫ የኤል ፋሸር ከተማን በእጁ ሲያስገባ አስደናቂ ድል አግኝቷል።
የእስራኤል እና የኢራን ግጭት
በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል የሆነችው የአይሁዶች አገር እስራኤል እንዴት ተመሠረተች?
በመካከለኛው ምሥራቅ ኃያል እና ብቸኛዋ የአይሁዶች አገር የሆነችው እስራኤል በዙሪያዋ ካሉ አገራት ሁሉ በዕድሜ ትንሿ ናት። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላ በአውሮፓውያኑ 1948 የእስራኤል እንደ አገር መመሥረት በአካባቢው አሁን ድረስ እየተካሄደ ያለ ለውጥን አስከትሏል። ለመሆኑ በየዕለቱ የዓለም መገናኛ ብዙኃን ስሟን ሳያነሱ የማያልፏት ይህች አገር እንዴት ተመሠረተች?
እስራኤል 15 የጦር አውሮፕላኖችን አሰማርታ ኳታር ውስጥ የፈጸመችው ጥቃት
በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ ውስጥ እስራኤል ጥቃት የፈጸመችው በርካታ የሐማስ ፖለቲካ ቢሮ ባለሥልጣናት በሚኖሩበት የመኖሪያ አካባቢ ላይ ነው። በዚህ ጥቃት አስከ ስምንት የሚደርሱ ፍንዳታዎችን እና ከፍተኛ ጭስ በዶሃ ሰሜናዊ ክፍል ላይ ማየታቸውን ዓይን እማኞች ተናግረዋል። ከጥቃቱ ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ እስራኤል ለተፈጸመው ጥቃት በይፋ ኃላፊነቱን ወስዳለች።
የእስራኤል ፕሬዝዳንት እንዲሆን ተጠይቆ የነበረው ታዋቂው የፊዚክስ ሊቅ አልበርት አንስታይን
የጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ቤን ጉርዮን መንግሥት በዓለም ታዋቂ የሆነው ሳይንቲስት አልበርት አንስታይን ለእስራኤል ፕሬዝዳንትነት እንዲሆን ካጩት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ የእስራኤል አምባሳደር አባ ኢባን አንስታይንን እንዲያነጋግሩ ተደረገ።
ሐማስ በጋዛ ከሚደረገው ጦርነት ተርፎ ኅልውናው ሊቀጥል ይችላል?
ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው ጦርነት በጋዛ ሰርጥ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ የግዛቲቱ አብዛኛው ክፍል ፈራርሷል። እስራኤል ዘመቻዋን ስትጀምር ያስቀመጠቻቸው ታጋቾችን የማስለቀቅ እና ሐማስን የመደምሰስ ዕቅዷ ከግቡ አልደረሰም። ከወዳጆቿ ሳይቀር ተቃውሞ ቢገጥማትም አሁን ደግሞ ጋዛን ሙሉ ለሙሉ የመቆጣጠር ዕቅድ እንዳላት ይፋ አድርጋለች። በርካታ መሪዎቹ የተገደሉበት ሐማስ ከዚህ ጦርነት በኋላ ዕጣ ፈንታው ምን ሊሆን ይችላል?
በእስራኤል ጥቃት እየተፈተኑ በሥልጣን ላይ አንድ ዓመት የሆናቸው የኢራኑ ፕሬዝዳንት
ማሱድ ፔዜሽኪያን ሐምሌ 2024 የኢራን ፕሬዝዳንት ሆነው ከተሾሙ ከአንድ ቀን በኋላ በቀጥታ ወደ ፖለቲካ እሳት ውስጥ ገብተዋል። ይህም አለመረጋጋት በሌለው በኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መሪዎች ታሪክ ውስጥ ከታዩት ጅማሪዎች መካከል እጅግ አስደንጋጩ እና በቀውስ የታጀበ ነበር።
በአሜሪካ ድጋፍ የተጀመረው የኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም ታሪክ
በአውሮፓውያኑ መጋቢት 5/1957 ዩናይትድ ስቴትስ በወቅቱ በመሐመድ ሬዛ ፓህላቪ ከምትመራው ኢራን ጋር ለሲቪል የአውቶሚክ ኢነርጂ አጠቃቀም የትብብር ስምምነት ተፈራረመች። በ'አተምስ ፎር ፒስ' መርሃ ግብር ጥላ ስር የነበረው ይህ ስምምነት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለመጀመር መሠረት ጣለ። ለዋሽንግተን፣ በዚያ የቀዝቃዛ ጦርነት ወቅት ኢራን ተጨማሪ መስህብ ነበራት።
የተመለሱ ጥያቄዎች
መጥፎ ጓደኛ ላለመሆን የሚረዱ አምስት ቀላል መንገዶች
እንዲኖረን የምንፈልገው ዓይነት ጓደኛ ለመሆን ማሻሻል ያለብን ባህሪዎች የትኞቹ ናቸው? እንዴትስ መጎ ጓደኛ መሆን ይቻላል? እነዚህ የብዙዎች ጥያቄ ናቸው።አንደኛው ጥሩ ጓደኛ መሆን የሚቻልበት መንገድ ተቃራኒ ማንነትን ማስወገድ ነው። ቋሚ መሆንን ጨምሮ በጎ ወዳጅ መሆን የሚቻልባቸውን መንገዶች እንመልከት።
በደቡብ ኢትዮጵያ ለሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ማርበርግ ቫይረስ መሆኑ ታወቀ፤ ክትባት ወይም መድኃኒት አለው?
በደቡብ ኢትዮጵያ በጂንካ ከተማ ተከስቶ ለስድስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው በሽታ ማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከኢትዮጵያ በስተደቡብ በሚገኙ አገራት ውስጥ ተከስቶ የነበረው ይህ በሽታ ከሳምንት በፊት ነው በደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ተከስቶ ሁለት የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎችን የገደለው።
ፎጣዎቻችን ለተለያዩ በሽታዎች ሊያጋልጡን እንደሚችሉ ያውቃሉ? እንዴት ንጽህናቸውን እንጠብቅ?
ሰውነታችንን አሊያም እጃችንን የምንደርቅባቸው ፎጣዎች ብዙ ጠቀሜታ ቢሰጡም እግረ መንገዳቸውን ረቂቅ ተህዋስያንን ከሰውነታችን ላይ ያነሳሉ።ፎጣዎቻችን ለምን ዓይነት በሽታዎች ያጋልጡናል? ፎጣዎችን ሳናጥብ ለምን ያህል ጊዜ እንጠቀምባቸዋለን? በምን ያህል ጊዜስ መታጠብ አለባቸወ?
የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት ምንድን ነው?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የእድሳት ሥራው የተጠናቀቀውን የፋሲል ግንብ መርቀዋል። ባለፈው ዓመት የጥገና እድሳት እየተከናወለት በነበረበት ወቅት የግንቡ ታሪካዊ ሽሯሟ ቀለም ነጥቶ መታየቱ በርካታ መላምት እንዲሰጥ አድርጎ ነበር። የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ በወቅቱ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ በማድረግ ለጉዳዩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ሌላ ዕይታ
ቢቢሲ አማርኛን በማኅበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉ
ከማኅደራችን
"ቢገድሉኝ ይሻል ነበር"፡ የሴቶችን ሕይወት እያበላሸ ያለው የተዘነጋው የአማራ ክልል ጦርነት
ከሁለት ዓመት በላይ የሆነው በአማራ ክልል በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚካሄደው ግጭት ሰላማዊ ሰዎች ከባድ ዋጋ እየከፈሉ ነው። ግጭቱ በሰው ሕይወት እና በንብረት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት ባሻገር በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት እና ሰቆቃ ትኩረትን አላገኘም። ቢቢሲ ለወራት ባካሄደው ክትትል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሴቶች የመደፈር እና የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ መሆናቸውን መረጃ አግኝቷል።
በብርሌ ፍቅር የወደቁት ፈረንጅ 'ብርሌ ውስጥ የኢትዮጵያ ታሪክ አለ' ይላሉ
ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ 'ብሔራዊ አጀንዳ' የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።
ዓለምን የሚዞረው ኢትዮጵያዊ ከዩቲዩብ ምን ያህል ያገኛል?
ከተከፈተ በዚህ ወር 20 ዓመት የሆነው የቪዲዮ ማጋሪያው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ዩቲዩብ ለብዙዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን ፈጥሯል። ከእነዚህም መካከል አቤል ብርሃኑ አንዱ ነው፤ በዩቲዩብ አማካኝነት 62 ሀገራትን ዟሯል። ያልረገጠው አህጉር አንታርቲካን ብቻ ነው። ሁሉንም የአሜሪካ ግዛቶች አካሏል። ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ዩቲዩብ ላይ የቆየው አቤል ከዩቲዩብ ምንያህል ያገኛል?
ቪዲዮ, በአርሰናል ‘ፍቅር የወደቁት’ የ65 ዓመቷ እናት፡ ወይዘሮ እቴቱ ማሞ, ርዝመት 3,29
ከእንግሊዝ ታላላቅ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው የአርሰናል የልብ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ እቴቱ ማሞ የ65 ዓመት እናት ናቸው። ላለፉት 20 ዓመታት አርሰናልን ያለማቋረጥ ደግፈዋል። እንደብዙዎቹ የቡድኑ ደጋፊዎች ዘንድሮ አርሰናል ዋንጫ ባለማንሳቱ ቢከፉም ድጋፋቸው ግን እንደሚቀጥል ይናገራሉ። ከሁሉም ተጫዋቾች ይልቅ እሳቸው ገብረኢየሱ ለሚሉት ለጋብሬል ጀሱስ እና ለቡካዮ ሳካ የተለየ ፍቅር አላቸው።
እነ ሞገስ አስገዶም፣ አብረሃ ደቦጭ፣ ፕ/ር አስራት ወልደየስ፣ ፕ/ር መስፍን ወ/ማሪያም፣ ስብሐት ገ/እግዚአብሔር የተማሩበት ተፈሪ መኰንን
ተፈሪ መኰንን ትምህርት ቤት ታሪክ የዘመናዊት ኢትዮጵያ ንድፍ እንደማለት ���ው። ላለፉት 100 ዓመታት ታላላቅ ሰዎችን ወልዷል። ለመኾኑ ይህ ተማሪ ቤት እነማንን አፈራ? ይህ ሐተታ በ100 ዓመት ታሪኩ ውስጥ በአንድም ሆነ በሌላ አሻራቸውን ያሳረፉትን ግለሰቦች ያወሳል፤ ከካናዳዊያን ጄስዊቶች እስከ ከንቲባ አዳነች አበቤ፤ ከቱጃሩ ራስ ኃይሉ ተክለሃይማኖት እስከ ቢሊየነሩ ሼክ አላሙዲን፣ ከሐኪም ወርቅነህ እሸቴ እስከ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ።
ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የምትገኘው አሊ ዶሮ እና አካባቢዋ ለምን የእገታ ማዕከል ሆኑ?
ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝብ እና በጭነት ተሽከርካሪዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እና እገታዎች ተበራክተዋል። ይህ ክስተት ደግሞ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በሚገኘው የሰሜን ሸዋ አካባቢ በተደጋጋሚ ሲከሰት ቆይቷል። በተለይ አሊ ዶሮ የሚባለው ቦታ የጥቃት እና የእገታ ማዕከል ሆኗል እየተባለ ነው። ቢቢሲ በተለይ ይህ ቦታ ለምን የመንገደኞች እና የአሽከርካሪዎች ‘የሞት ቀጣና’ ሆነ? በሚል ለወራት የዘለቀ ምርመራ አድርጓል።
ባይተዋር ከተማ፡ “ፒያሳ፣ ካዛንቺስ... ሰፈሬ አልመስል አሉኝ”
ባለፉት ዓመታት በአዲስ አበባ በቅርስነት ተመዝግበው የነበሩ እንዲሁም ሌሎችም ታሪካዊ ሕንጻዎች፣ ቤቶች እና አካባቢዎች እንደ ዋዛ አፈር ለብሰዋል። በዚህ ዘገባ፣ አንድን ሕንጻ ወይም ቤት ቅርስ አልያም ታሪካዊ ሥፍራ ለማለት መስፈርቱ ምንድን ነው? የታሪካዊ ሕንጻዎች እና ቤቶች መፍረስ በታሪክ፣ በነዋሪዎች ሥነ ልቦና፣ በኪነ ሕንጻ እና በማኅበራዊ መስተጋብር ላይ ምን ጫና ያሳድራል? ቅርሶች እና ታሪካዊ ሥፍራዎችን እንዴት ጠብቆ ማደስ፣ ማዘመን፣ መልሰው አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ማድረግ እንዲሁም ከሌሎች ግንባታዎች ጋር ጎን ለጎን እንዲሄዱ ማድረግ ይቻላል? የሚሉት እና ተያያዥ ነጥቦች ተዳስሰዋል።
“ሰው መሃል ሆኜ ሁሉም ጨካኝ ሆኖብኝ ነበር” - የፀጋ በላቸው ዘጠኝ የጠለፋ ቀናት
ግንቦት 2015 ዓ.ም. የተፈጸመው የፀጋ በላቸው ጠለፋ ብዙዎችን ያስቆጣ፣ መነጋገሪያም የሆነ የወንጀል ድርጊት ነበር። ፀጋ፤ ከአንድ ዓመት ከመንፈቅ በፊት ተጠልፋ ያሳለፈቻቸውን ቀናት በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቢቢሲ በዝርዝር ተናግራለች። ከቢቢሲ ጋር በነበራት ዘለግ ያለ ቆይታ፤ ስለተጠለፈችበት መንገድ እና ስላሳለፈቻቸው ዘጠኝ ቀናት በዝርዝር ተርካለች። ከጠለፋው ነጻ የወጣችበት መንገድም አስቀድሞ በክልሉ መንግሥት ከተገለጸው የተለየ እንደሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናግራለች። ለምን ከኢትዮጵያ እንደተሰደደች እና ስለ ቀጣይ ዕቅዶቿም እንዲሁ አጋርታለች።
". . . ከምድሩ ይልቅ የሰማዩን መንገድ ለመምረጥ ተገደናል" እገታ ያሰጋቸው መንገደኞች
ባለፉት ዓመታት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ውስጥ የሚካሄዱ ግጭቶች እና በታጣቂዎች የሚፈጸሙ እገታዎች ዜጎች በፈለጉት ጊዜ እና መንገድ በአገሪቱ ውስጥ እንዳይንቀሳቀሱ ብርቱ ስጋት ፈጥሮባቸዋል። በተለይ ደግሞ የመንገደኞች ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን በማድረግ የሚፈጸሙት ያላባሩ እገታዎች በዋነኞቹ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ እንቅስቃሴን አዳጋች አድርገውታል። በዚህም ሳቢያ አቅሙ ያላቸው እና የግድ የሆነባቸው ሰዎች ፊታዎችን ወደ አየር ትራንስፖርት አዙረዋል።
የአእምሮ ዕድገት መዛባት (ኦቲዝም) ያለባቸው መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚረዳ ጥናት ለኳታር ያቀረቡት ኢትዮጵያዊ ተመራማሪ
ዛሬ፣መጋቢት 24 የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን ነው። ይህ ዕለት በዓለም ደረጃ ታስቦ እንዲውል ለተባበሩት መንግሥታት ሐሳብ ያቀረበችው ኳታር ናት። ወደዚያው ብናቀና ዶክተር ወንድወሰን ግርማን እናገኛለን። ኦቲስቶች መኪና እንዲያሽከረክሩ የሚያስችል ከፍተኛ ምርምር ያደረጉ ኢትዮጵያዊ ናቸው።
'ዝምተኛው ገዳይ' በኢትዮጵያ
የዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የአየር ብክለት ል���ት ከፍተኛ መሆኑን ያሳያል። ድርጅቱ እንደሚለው 99 በመቶው የዓለም ሕዝብ የሚተነፍሰው አየር ተበክሏል። ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የሚዳርገው የአየር ብክለት በኢትዮጵያ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ባለሙያ ይናገራሉ። ለመሆኑ በኢትዮጵያ ዋነኛ አየር በካዮች የትኞቹ ናቸው? መፍትሔውስ ምንድን ነው?