በዩክሬን እና ሩሲያ የሰላም ድርድር ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ የሚገኙት እነማን ናቸው?

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም በሚደረገው ስምምነት ላይ የአሜሪካ ልዑካን ቡድን ከሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለመነጋገር ወደ ክሬምሊን አቅንተዋ���።
ጉዞው በዩክሬን ጉዳይ ላይ ስምምነት ላይ ለመድረስ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ውስጥ የቅርብ ጊዜው እርምጃ ነው።
ከሁለት ሳምንታት በፊት አሜሪካ ለሩሲያ ያደላ እንደሆነ በሰፊው የተነገረ 28 ነጥብ ያለው የሰላም ዕቅድ ለኪየቭ አቅርባለች።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በጄኔቫ እና ፍሎሪዳ የአሜሪካ-ዩክሬን ውይይት ተደርጓል።
ነገር ግን በውይይቱ ውስጥ የተሳተፉት ቁልፍ ተደራዳሪዎች እነማን ናቸው?

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
አሜሪካ፡ ዳን ድሪስኮል
የ39 ዓመቱ ድሪስኮል በታሪክ ትንሹ የአሜሪካ ጦር ዋና ፀሐፊ እንዲሁም የምክትል ፕሬዝዳን ጄዲ ቫንስ የቀድሞ የክፍል ጓደኛ እና የቅርብ አጋር ናቸው።
የአሜሪካ የሰላም ዕቅዶች ሾልከው ከወጡ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፤ ባለፈው ወር በዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ በተደረገ ልዑክ ውስጥ በድንገት ከተካተቱ በኋላ ጦርነቱን ለማስቆም በሚደረገው ድርድር ውስጥ ማዕከላዊ ሰው ሆነዋል።
ድሪስኮል የወደፊት የአሜሪካ የመከላከያ ፀሐፊ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተነግሯል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው መጀመሪያ ላይ የጦር ሠራዊት ፀሐፊ አድርገው ሲሾሟቸው፣ "የለውጥ ወኪል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ የልምድ ጥምረት እንዳለባቸው" ተናግረዋል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
አሜሪካ፡ ስቲቭ ዊትኮፍ
የትራምፕ የሪል ስቴት እና የጎልፍ አጋር የሆኑት ዊትኮፍ መጀመሪያ ላይ በመካከለኛው ምሥራቅ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ተሹመዋል ነገር ግን የአሜሪካ ከሩሲያ ጋር በሚደረገው ድርድር ቁልፍ አካል ሆነዋል።
ጦርነቱን ለማስቆም የሞስኮን ጥያቄዎች ቅድሚያ በመስጠት ትችት ይቀርብባቸዋል፤ እና በዚህ ዓመት ወደ ኪየቭ ሳይሄዱ የሩሲያ ዋና ከተማን ብዙ ጊዜ ጎብኝተዋል።
ይህ ፑቲንን ለማግኘት ወደ ሞስኮ ያደረጉት ስድስተኛ የታወቀ ጉብኝታቸው ነው።

የፎቶው ባለመብት, PA/Getty Images
አሜሪካ፡ ማርኮ ሩቢዮ
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የአገሪቱ ከፍተኛ ዲፕሎማት የሆኑት ሩቢዮ በጄኔቫ የአሜሪካን ልዑክ መርተዋል፤ የቅርብ ጊዜው የሰላም ዕቅዱ ረቂቅ ማሻሻያዎችን አድርገዋል።
በታሪክ ውስጥ በትራምፕ አስተዳደር ውስጥ ካሉ ሌሎች ሰዎች ይልቅ ሩሲያን የበለጠ የሚተቹ ናቸው ይባላሉ።
በፍሎሪዳ በተካሄደው የሰላም ድርድር ቅዳሜና እሁድ ላይ ንግግር ሲያደርጉ፣ የቅርብ ጊዜው የዲፕሎማሲ ዙር "ጦርነትን የሚያቆሙ ውሎችን ብቻ አይደለም" ብለዋል።
"ለዩክሬን የረጅም ጊዜ ብልጽግና ውሎችም ጭምር ነው... ዛሬ በዚያ ላይ እንደሰራን አስባለሁ፣ ግን ብዙ የሚቀር ጉዳይ አለ።"

የፎቶው ባለመብት, Reuters/Getty Images
አሜሪካ፡ ያሬድ ኩሽነር
ኩሽነር የትራምፕ አማች ሲሆን በፕሬዚዳንቱ የመጀመሪያ የሥልጣን ዘመን እንደ ከፍተኛ አማካሪ ቁልፍ ሰው ነበር።
በዓለም አቀፍ የንግድ ግንኙነቶች እና በንብረት ልማት ይታወቃል።
የ44 ዓመቱ ሰው በዚህ ጊዜ በትራምፕ አስተዳደር ውስጥ ኦፊሴላዊ ሚና ባይጫወትም፣ በዚህ ሁለተኛ የሥልጣን ዘመን በዋይት ሐውስ የዲፕሎማሲያዊ ውይይቶች ወቅት እንደ አማካሪ ሆኖ ያገለግላል።
በቅርቡ በዩክሬን የሰላም ድርድር ውስጥ እየተሳተፈ ነው።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ዩክሬን፡ አንድሪ ዬርማርክ (አሁን ከሥልጣን ለቅቀዋል)
ባለፈው ሳምንት በፀረ-ሙስና ዘመቻ ከተደረገ በኋላ ከሥልጣናቸው ከመልቀቃቸው በፊት፣ ዬርማክ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪ የረዥም ጊዜ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የአገሪቱ ዋና ተደራዳሪ ነበሩ።
የጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ እንደመሆናቸው መጠን፣ በመንግሥት ከፍተኛ ቦታ ላይ ከፍተኛ ሥልጣን ነበራቸው እና ወሳኝ የሰላም ድርድሮችን እንዲመሩ በዘሌንስኪ ተሹመዋል።
ባለፈው ሳምንት የፀረ-ሙስና መርማሪዎች በኪየቭ የሚገኘውን ቤታቸው ከወረሩ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የፖለቲካ ስራቸው በድንገት አክትሟል።

የፎቶው ባለመብት, EPA/Getty Images
ዩክሬን፡ ሩስቴም ኡሜሮቭ
ኡሜሮቭ የዩክሬን ብሔራዊ የጸጥታ ምክር ቤት ኃላፊ ናቸው። ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በፍሎሪዳ በተካሄደው ውይይት የዩክሬን ዋና ተደራዳሪ ሆነው ዬርማክን ተክተዋል።
በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ የሰላም ድርድር ልምድ አላቸው እስካለፈው ሐምሌ ወር ድረስ የዩክሬን የመከላከያ ሚኒስትር ነበሩ።
ኡሜሮቭ በውይይቱ ዬርማክን መተካት ለኪየቭ የሚኖረው አስተዋጽዖ አሉታዊ ነው ወይስ አዎንታዊ የሚለው ግልጽ አለመሆኑን የቢቢሲ የዩክሬን ዘጋቢ ጄምስ ዋተርሃውስ ተናግሯል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ሩሲያ፡ ኪሪል ዲሚትሪቭ
ዲሚትሪቭ ትራምፕ ሁለተኛውን የፕሬዚዳንትነት ዘመን ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ የአሜሪካ እና ሩሲያ ��ፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች አካል ናቸው።
ከዚህ በፊት በአሜሪካ ሰርተዋል፤ ኖረዋልም፤ እንዲሁም ከውጭ ዲፕሎማሲ ወይም ከወታደራዊ ኃይል ይልቅ በንግድ ስምምነቶች የበለጠ ልምድ አላቸው።
ከአብዛኛዎቹ የፑቲን አባላት በተለየ መልኩ፣ በአሜሪካ የቴሌቪዥን ስቱዲዮ ውስጥ ቃለ መጠየቅ ለመስጠት አያመነቱም። የትራምፕን የዲፕሎማሲ ክህሎቶች በማመስገን ለምዕራባውያን ተመልካቾች የሩሲያ መንግሥትን ትረካ በራሳቸው ቋንቋ ይሰጣሉ።
ባለፈው ወር የወጣው የሰላም እቅድ ረቂቅ የመጣው በማያሚ ዲሚትሪቭ እና ዊትኮፍ ለሦስት ቀናት ከተገናኙ በኋላ ነው።

የፎቶው ባለመብት, Reuters/Getty Images
ሩሲያ፡ ዩሪ ኡሻኮቭ
ኡሻኮቭ እአአከ2012 ጀምሮ ቭላድሚር ፑቲንን በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ላይ ሲያማክሩ ቆይተዋል፤ ከ1998 እስከ 2008 የሩሲያ የአሜሪካ አምባሳደር ነበሩ።
ብሉምበርግ ኒውስ እንደዘገበው ከዊትኮፍ ጋር ባደረጉት እና ሾልኮ በወጣ የስልክ ጥሪ ትራምፕ ድርድሩን ለማስቀጠል ከፑቲን ጋር እንዲነጋገሩ ፍላጎት እንዳላቸው ታይቷል።
ባለፈው ሳምንት በሞስኮ "የአውሮፓ ዕቅድ፣ በመጀመሪያ ሲታይ... ሙሉ በሙሉ ገንቢ ያልሆነ እና ለእኛ የማይሰራ ነው" ብለዋል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters/Getty Images
ሩሲያ፡ ቭላድሚር ሜዲንስኪ
ከፑቲን ከፍተኛ ረዳቶች አንዱ የሆኑት ሜዲንስኪ፣ የዩክሬን ሙሉ ወረራ በ2022 ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የሩሲያ የድርድር ቡድን ቁልፍ አባል ናቸው።
የቀድሞው የባህል ሚኒስትር ለጦርነቱ አሳማኝ ምክንያት እንዲኖር የረዱ ጠንካራ ሰው በመባል ይታወቃሉ።
በማዕከላዊ ዩክሬን በምትገኘው ስሚላ ከተማ ነው የተወለዱት















